Saturday, April 21, 2012

እኮ መች ሰደበን አልን...?


ከህዝብ ልጅ በፊት ብዙዎች አዚሙ
ምኒሊክ ጀግና ነው ብለው ደጋገሙ
ማን ገዶት ማንስ ጆሮ ሰጥቶት ለዛ ዳንኪራቸው
ያሻቸውን ቢሎ ሁሉም self opinion entitle ናቸው
ግና የህዝብ ልጅ የህዝብ ነውና
እርሱ ራሱን ሊሰጥ በምላሹ ክብር ይሰጥዋልና
ያማ  ነው ውለታው ሌላማ ምን አለ
ጥቁር ሰው ጥቁር ሰው ብሎ ሊያስታርቀን ከመድረኩ ሳለ
እረ እኛ አላልንም የህዝብ ልጅ ሰደበን
ታሪኩም ታሪካችን ድሉም ያአፍሪካ ድል ብለን መሰከርን
ነገሩ ወዲህ ነው አይደለም ከወዲያ
ታሪክ ጸሃፊዎቻችን ተጠምደው በጥድፊያ
በመረጣ ስልት በመተው በሽታ በታሪክ ማጠልሸት
ይህው አገር ሰጡን የአንዱ ታሪክ ገዝፎ የሌላው የሞተበት
ምን አለበት ታድያ እኛም እንደናንተ self opinion entitle ብንሆን?
አቦቦቦ!!! ተውን በቃ ጥቁር ሰው አይደለም ጥቁር ልብ ይጥፋልን

1 comment:

Anonymous said...

good poem